tg-me.com/Wahidcom/3719
Last Update:
ሙቀረቡን
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
56፥11 እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡ أُولَـٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ
"ሙቀረብ" مُقَرَّب የሚለው ቃል "ቀሪበ" قَرِبَ ማለትም "ቀረበ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ቀራቢ" "ባለሟል" ማለት ነው፥ "ሙቀረቡን" مُقَرَّبُون ወይም "ሙቀረቢን" مُقَرَّبِين ደግሞ የሙቀረብ ብዙ ቁጥር ሲሆን "ቀራቢዎች" "ባለሟሎች" ማለት ነው። ከአስሓቡል የሚን ለበጎ ሥራ ቀዳሚዎቹ ለገነት ቀዳሚዎች ሲሆኑ እነርሱ አሏህ ዘንድ "ሙቀረቡን" ናቸው፦
56፥11 እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡ أُولَـٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ
የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ሲሆን እነርሱም "ሙቀረቡን" ናቸው፦
83፥21 "ባለሟልዎቹ" ይጣዱታል፡፡ يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ
83፥28 "ባለሟሎቹ" ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡ عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ
አንድ አማኝ ካመነ በኃላ የሚሠራው መልካም ሥራ ወደ አሏህ መቃረቢያ ሲሆን "ቁርባን" ይባላል፥ "ቁርባን" قُرْبَان ማለት "መቃረቢያ" ማለት ነው፦
5፥35 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህን ፍሩ! ወደ እርሱም መቃረቢያ መልካም ሥራን ፈልጉ፡፡ ትድኑ ዘንድም በእርሱ መንገድ ታገሉ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَابْتَغُوا إِلَيْهِ الْوَسِيلَةَ وَجَاهِدُوا فِي سَبِيلِهِ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
9፥99 ከአዕራቦችም በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን፣ የሚሰጣቸውን ምጽዋቶች አሏህ ዘንድ መቃረቢያዎች እና ወደ መልእክተኛው ጸሎቶች መዳረሻ አድርጎ የሚይዝ ሰው አለ፡፡ ንቁ! እርሷ ለእነርሱ በእርግጥ አቃራቢ ናት፥ አሏህ በችሮታው ውስጥ (በገነቱ) በእርግጥ ያስገባቸዋል፡፡ አሏህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ وَمِنَ الْأَعْرَابِ مَن يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَيَتَّخِذُ مَا يُنفِقُ قُرُبَاتٍ عِندَ اللَّهِ وَصَلَوَاتِ الرَّسُولِ ۚ أَلَا إِنَّهَا قُرْبَةٌ لَّهُمْ ۚ سَيُدْخِلُهُمُ اللَّهُ فِي رَحْمَتِهِ ۗ إِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيمٌ
"አዕራብ" أَعْرَاب ማለት "ገጠሬ" ማለት ሲሆን ከዐረብ ገጠሬዎች በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን አምነው የሚሰጣቸውን ምጽዋቶች አሏህ ዘንድ መቃረቢያዎች አድርገው የሚይዙ ሰዎች አሉ፥ ስለዚህ አሏህ ዘንድ ከሰዎች መካከል ሙቀረቡን አሉ። በተመሳሳይ መላእክት የአሏህ ባመሟሎች ስለሆኑ "ሙቀረቢን" مُقَرَّبِين ተብለዋል፦
4፥172 አልመሢሕ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ "ቀራቢዎች" የኾኑት መላእክት አይጠየፉም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ
መላእክት ወደ መርየም መጥተው ለመርየም ያሏት "ባለሟል በኾነ ልጅ" ሳይሆን "ከባለሟሎችም በኾነ ልጅ" የሚል ነው፦
3፥45 መላእክት ያሉትን አስታውስ፡- «መርየም ሆይ! አሏህ ከእርሱ በኾነው ቃል ስሙ አልመሢሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለም እና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ልጅ ያበስርሻል»። إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِّنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አል ሙቀረቢን" الْمُقَرَّبِين የተባሉ ከላይ እንደተገለጸው የአሏህ ባሮች ሲሆኑ ይህ አንቀጽ ጭራሽኑ ከሙቃሪቢን መካከል አንዱ ዒሣ መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፥ "ዒሣ ብቻ "ባለሟል" ነው" የሚል ሽታው ቁርኣን ላይ የለም። አምላካችን አሏህ ሙቀረቡን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/us/ወሒድ የንጽጽር ማኅደር/com.Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
BY ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/Wahidcom/3719