tg-me.com/fezekiru/1525
Last Update:
አንዳንዴ ሽንፈትን፣ ስብራትን መቀበል እና ማመን ተገቢ ነው። ጥንካሬ ማለት ሽንፈትን ወይም ህመምን መካድ ማለት አይደለም። ከህመም እና ሽንፈቱ ገዝፎ መገኘት እንጂ! ባልነቁ ሀሳቦች ለማነቃቃት የሚዳክሩ ብዙ ናቸው። አሸናፊነት ሁሌም አሸናፊ ነኝ፣ እችላለሁ በማለት ብቻ አይገኝም። ተጎድተህ ከነበር ጉዳትህን አምነህ ለማገገም ተጣጣር እንጂ አልተጎዳሁም በማለት ከጎዳህ ነገር በላይ እራስህን አትጉዳ! ጥለውሽ ሄደዋል ወይም የሆነ ክብርሽን ዝቅ ባደረገ ምክንያት ከተለዩሽ አምነሽ ተቀበይ። እኔ እራሴ ተውኳቸው፣ አልፈለግኳቸውም እያልሽ በውሸት ምክንያቶችሽ ጭስ አትታፈኝ።
ሰው መሆናችንን አንዘንጋ እንጂ! ሰው የከፍታ እና ዝቅታ ቅይጥ ነው። እንባሽን ዋጥ አድርገሽ መሳቅ መቻልሽ አይደለም ጠንካራ የሚያስበብልሽ፣ ዘውትር የሚያስለቅስሽን ነገር አውቀሸወ መፍትሄ መፈለግሽ እንጂ! በአንድ ሰው ሰበብ ሁሉም ሰዎች ቆሻሻ እየመሰሉህ እንደ ዝንብ ማረፍ መቻልህ አይደለም ህመምህን የሚያስታግስልህ፣ የነጀሰህን ሰው ቆሻሻ አፅድተህ አንተም ሌሎችን ከመነጀስ ለመታቀብ መጣጣርህ ነው ህመምህን በደንብ የሚያሽረው።
እረፉ! አጓጉል ጠንካራ ነኝ በሚል ውስጥ ውስጡን አትሰበሩ። ሰላም ነኝ ምንም አልሆንኩም እያላችሁ የዛፍ ላይ እንቅልፍ አትተኙ! በቃ አጉል ሽንፈትና ጉዳታችሁን ላለማመን ችክ እያላችሁ የፈውሳችሁን ጊዜ አታርቁት! አንዳንድ ህመምና ጉዳቶች ተቀብለን ካላመንናቸው አይሽሩም። ግድየላችሁም በአጓጉል ያለማመን ትግላችሁ የተነሳ ወደ ጌትየው የምትዘልቁበትንም ጊዜ እርም አታድርጉት። ልብ በሉ አዕምሮ ደጋግመው የነገሩትን ሁሉ ፍፁም ሁሌም አይቀበልም። ልብም ደጋግመው ያሰቡትን ሁሉ አያፈቅርም። #አብሽሩ! ብቻ እንዲህ ይሰምማኛል!
@fezekiru
@fezekiru
BY አስታውስ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/fezekiru/1525