Telegram Group & Telegram Channel
"ማርያም እኮ ሞተች"
ኤልያስ ሽታኹን
*           *         *         *        *           
"የአብ ወዳጁ
የወልድ ደጁ
የቅዱስ መንፈስ እጁ፡፡"
                                ማርያም እኮ ሞተች፡፡

የአባጊዮረጊስ ዘጋስጫ
የማትወዳደር ምረጫ
የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴው
የቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴው
ዮሴፍ ሲገፍፍ የለበሳት
ያዕቆብ በልቡ ያነገሣት

                              ማርያም እኮ ሞተች፡፡
ገብርኤል ለብስራት
ወዴት ልላክ? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
የቱ ጋር ነች? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
እናትህ የቷ ናት? ብሎ ያልጠየቀው
በሚካኤል አክናፍ መልኳን ስለሚያውቀው፡፡
ሰማይን ያለባላ ያቆመ
ወንዳቺ ሆድ ያዘመመ
ጥንተ ናፍቆት
የመለኮት
ዓይንሽ የሰባቱ ሰማያት መስኮት፡፡
ያ ትሁት ገፅሽን
በክንፍ ላይ ስሎሽ መላእክት ያያሉ
ለምነውት ነበር ፍጠራት እያሉ፡፡
(ቶሎ በል እያሉ)

                                   ማርያም እኮ ሞተች፡፡

በመኑ በአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ
ነፍሴ ወዴት ደረስሽ? ማርያምን ሳትነኪ
አንቲ ውዕቱ
እኔ ምዑቱ
አንቲ መሶበ ወርቅ
እኔ የበደል ጨርቅ
አንቺ እመአምላክ
የቱ መግነዝ ቻለሽ
ትንሳኤን ወልደሽው ሞትን ትቀምሻለሽ?
አንቺም? እመብርሃን

                                      ማርያምእኮ ሞተች፡፡

ሰማይና ምድር
ወይቦ መልካቸው ሀዘን እያማጡ
እስከዛሬ አሉ
መላእክት ሁሉ እንደደነገጡ፡ 
ለክልዔቱ ጊዜ እስራኤል ጨነቀው
ከስደት ጀምሮ ኮቴዋን የሚያውቀው፡፡
የዳዊት በገና
ብቻውን ያለቅሳል ራሱን በመግረፍ
ዳዊት አላወቀም የልጅ ልጁን ማረፍ፡፡
ክልዔቱ ጊዜ ጨነቀው እስራኤል
እንኳንና አርፋ
ሲከፋት አይችልም በእርሷ እኮ ሚካኤል::
ክልዔቱ ጊዜ
ሰማይ አለቀሰ የመረረ ከሀሞት
መላእክት አያውቁም ማርያም እንደምትሞት፡፡

                               

                                           ማርያም እኮ ሞተች፡፡

ስትሰማ ኖሯ በሆዷ ቅዳሴ
አረፈች ይሉኛል  ወዮ ነው ለራሴ፡፡
አንቺን እመብርሃን ሞት በምኑ ያዘሽ
አላየሽም እንዴ አምላኩን እንዳዘዝሽ፡፡
የቱ መልአክ ሞት ተላከ ወዳንቺ
ችሎ አይገባም ቤትሽ እሺ ብለሽ እንጂ፡፡
ፍትሃት የለም ለማርያም
የተፈታ የሚገባባት እርሷ ራሷ አርያም፡፡
ለማርያም አይቀደስላት
እርሷ ራሷ ቅዳሴ ናት፡፡

                                        ማርያም እኮ ሞተች፡፡

*       *        *         *        *         *

#ማስታወሻ
   * በነገረ - ማርያም
   * ስንክሳርም እንደተነገረን
እመቤታችን በ፷፬ አመቷ  በገዛ ፍቃዷ አርፋ፡፡
ሞትን ቀምሳለች፡፡ነሐሴ ፲፮  ከሞት ተነስታ ማረጓን ልብ ይሏል፡፡
"ሞትሰ ለመዋቲ ለመዋቲ ይደሉ
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ"


@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb



tg-me.com/yeorthodoxmezmur/219
Create:
Last Update:

"ማርያም እኮ ሞተች"
ኤልያስ ሽታኹን
*           *         *         *        *           
"የአብ ወዳጁ
የወልድ ደጁ
የቅዱስ መንፈስ እጁ፡፡"
                                ማርያም እኮ ሞተች፡፡

የአባጊዮረጊስ ዘጋስጫ
የማትወዳደር ምረጫ
የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴው
የቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴው
ዮሴፍ ሲገፍፍ የለበሳት
ያዕቆብ በልቡ ያነገሣት

                              ማርያም እኮ ሞተች፡፡
ገብርኤል ለብስራት
ወዴት ልላክ? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
የቱ ጋር ነች? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
እናትህ የቷ ናት? ብሎ ያልጠየቀው
በሚካኤል አክናፍ መልኳን ስለሚያውቀው፡፡
ሰማይን ያለባላ ያቆመ
ወንዳቺ ሆድ ያዘመመ
ጥንተ ናፍቆት
የመለኮት
ዓይንሽ የሰባቱ ሰማያት መስኮት፡፡
ያ ትሁት ገፅሽን
በክንፍ ላይ ስሎሽ መላእክት ያያሉ
ለምነውት ነበር ፍጠራት እያሉ፡፡
(ቶሎ በል እያሉ)

                                   ማርያም እኮ ሞተች፡፡

በመኑ በአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ
ነፍሴ ወዴት ደረስሽ? ማርያምን ሳትነኪ
አንቲ ውዕቱ
እኔ ምዑቱ
አንቲ መሶበ ወርቅ
እኔ የበደል ጨርቅ
አንቺ እመአምላክ
የቱ መግነዝ ቻለሽ
ትንሳኤን ወልደሽው ሞትን ትቀምሻለሽ?
አንቺም? እመብርሃን

                                      ማርያምእኮ ሞተች፡፡

ሰማይና ምድር
ወይቦ መልካቸው ሀዘን እያማጡ
እስከዛሬ አሉ
መላእክት ሁሉ እንደደነገጡ፡ 
ለክልዔቱ ጊዜ እስራኤል ጨነቀው
ከስደት ጀምሮ ኮቴዋን የሚያውቀው፡፡
የዳዊት በገና
ብቻውን ያለቅሳል ራሱን በመግረፍ
ዳዊት አላወቀም የልጅ ልጁን ማረፍ፡፡
ክልዔቱ ጊዜ ጨነቀው እስራኤል
እንኳንና አርፋ
ሲከፋት አይችልም በእርሷ እኮ ሚካኤል::
ክልዔቱ ጊዜ
ሰማይ አለቀሰ የመረረ ከሀሞት
መላእክት አያውቁም ማርያም እንደምትሞት፡፡

                               

                                           ማርያም እኮ ሞተች፡፡

ስትሰማ ኖሯ በሆዷ ቅዳሴ
አረፈች ይሉኛል  ወዮ ነው ለራሴ፡፡
አንቺን እመብርሃን ሞት በምኑ ያዘሽ
አላየሽም እንዴ አምላኩን እንዳዘዝሽ፡፡
የቱ መልአክ ሞት ተላከ ወዳንቺ
ችሎ አይገባም ቤትሽ እሺ ብለሽ እንጂ፡፡
ፍትሃት የለም ለማርያም
የተፈታ የሚገባባት እርሷ ራሷ አርያም፡፡
ለማርያም አይቀደስላት
እርሷ ራሷ ቅዳሴ ናት፡፡

                                        ማርያም እኮ ሞተች፡፡

*       *        *         *        *         *

#ማስታወሻ
   * በነገረ - ማርያም
   * ስንክሳርም እንደተነገረን
እመቤታችን በ፷፬ አመቷ  በገዛ ፍቃዷ አርፋ፡፡
ሞትን ቀምሳለች፡፡ነሐሴ ፲፮  ከሞት ተነስታ ማረጓን ልብ ይሏል፡፡
"ሞትሰ ለመዋቲ ለመዋቲ ይደሉ
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ"


@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb

BY የorthodox መዝሙር ብቻ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/yeorthodoxmezmur/219

View MORE
Open in Telegram


የorthodox መዝሙር ብቻ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

China’s stock markets are some of the largest in the world, with total market capitalization reaching RMB 79 trillion (US$12.2 trillion) in 2020. China’s stock markets are seen as a crucial tool for driving economic growth, in particular for financing the country’s rapidly growing high-tech sectors.Although traditionally closed off to overseas investors, China’s financial markets have gradually been loosening restrictions over the past couple of decades. At the same time, reforms have sought to make it easier for Chinese companies to list on onshore stock exchanges, and new programs have been launched in attempts to lure some of China’s most coveted overseas-listed companies back to the country.

In many cases, the content resembled that of the marketplaces found on the dark web, a group of hidden websites that are popular among hackers and accessed using specific anonymising software.“We have recently been witnessing a 100 per cent-plus rise in Telegram usage by cybercriminals,” said Tal Samra, cyber threat analyst at Cyberint.The rise in nefarious activity comes as users flocked to the encrypted chat app earlier this year after changes to the privacy policy of Facebook-owned rival WhatsApp prompted many to seek out alternatives.የorthodox መዝሙር ብቻ from us


Telegram የorthodox መዝሙር ብቻ
FROM USA